የጋምቤላ ከተማ አቀማመጥ ሜዳማ እና አነስተኛ ጋራዎች ያሉባት እንዲሁም በባሮ ወንዝ ዳር የሚትገኝ በመሆኗ ለወደፊት እድገቷ ከፍተኛ ነው፡፡ የባሮ ወንዝ ከተማዋን መሀል ለመሃል ሰንጥቆ የሚፈስ በመሆኑ ለከተማዋ ትልቅ የልማት ሀብት ነው፡፡

 የጋምቤላ ከተማ የአየር ፀባይ አማካይ የሙቀት መጠን 28.3 ዲግሪ ሴልሺየስ ያላት ብትሆንም ማንኛውም የከተማዋ ነዋሪ በሚኖርበት አከባቢ በመንገድ ዳር እንዲሁም በመኖሪያ ቤት አከባቢ ዛፍ የመትከል ልምድ ስላለው ዓመቱን በሙሉ በአረንጓዴ የተሸፈነች ነች፡፡